Home Back

የትግራይ ክልል አርሶ አደሮች ከፍተኛ የማዳበሪያ እጥረት ላይ መሆናቸውን ገለጹ

voanews.com 2024/10/6
ፎቶ ፋይል፦ መቀሌ
ፎቶ ፋይል፦ መቀሌ

በትግራይ ክልል፣ በአፈር ማዳበሪያ እና በፀረ ተባይ ኬሚካል አቅርቦት ከፍተኛ ውስንነት እንደሚታይ ያመለከቱ አርሶ አደሮች፣ ጦርነት እና ድርቅ ካስከተሉባቸው ችግሮች በተጨማሪ በግብአት እጥረቱ የመኸር ወቅት ምርታማነቸው እንዳይጎዳ ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

በክልሉ የአፈር ማዳበሪያ ስርጭቱ ከሚያስፈልገው በእጅጉ ያነሰ እንደኾነ የገለጸው ተቃዋሚው ሣልሳይ ወያኔ ፓርቲም፣ አሳሳቢ ሲል የገለጸውን የማዳበሪያ እጥረት በአፋጣኝ ለመቅረፍ፣ የረድኤት ድርጅቶች የበኩላቸውን እገዛ እንዲያደርጉ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል፡፡

የክልሉ የግብርና እና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ በበኩሉ፣ እስከ አሁን ከ430ሺሕ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ወደ ክልሉ መግባቱን አስታውቆ፣ “አቅርቦቱ ካለፉት ዓመታት የበለጠና መሻሻል የታየበት ነው” ብሏል፡፡

People are also reading