Home Back

በሐብሩ ወረዳ የተኩስ ልውውጥ ባልታጠቁ ነዋሪዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱ ነዋሪዎች አስታወቁ

voanews.com 2024/7/5
 በሰሜን ወሎ ዞን ሐብሩ ወረዳ ውርጌሳ ከተማ አካባቢ
በሰሜን ወሎ ዞን ሐብሩ ወረዳ ውርጌሳ ከተማ አካባቢ

በሰሜን ወሎ ዞን ሐብሩ ወረዳ ውርጌሳ ከተማ አካባቢ፣ ባለፈው ሳምንት ኀሙስ፣ በመከላከያ ኀይል እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ፣ ባልታጠቁ ሰዎች ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱን ነዋሪዎች አስታወቁ።

በከተማው የጸጥታ ችግር እንደነበርና የተጎዱም ሰዎች መኖራቸውን የጠቀሰው የሐብሩ ወረዳ አስተዳደር፣ አኀዛዊ መረጃ ለመስጠት ግን በምርመራ ላይ መኾኑን ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል፡፡

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

ከውርጌሳ ከተማ በተጨማሪ፣ በተለያዩ የሐብሩ ወረዳ አቅራቢያዎችም የጸጥታ ችግር እንደሚስተዋል የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው ሑሴን መሐመድ፣ በሕዝቡ ዕለታዊ ኑሮ ላይ ጫና መፍጠሩን አመልክተዋል።

People are also reading