Home Back

የባሕር ዳር የሰላም ኮንፈረንስ ተሳታፊዎች የግጭት ታሳሪዎች እንዲፈቱ ጠየቁ

voanews.com 2024/7/7
የዐማራ ክልል ርእሰ መዲና ባሕር ዳር ከተማ
የዐማራ ክልል ርእሰ መዲና ባሕር ዳር ከተማ

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

በትጥቅ ግጭት ውስጥ በሚገኘው የዐማራ ክልል ርእሰ መዲና ባሕር ዳር ከተማ፣ ላለፉት ሁለት ቀናት የተካሔደውን የሰላም ጉባኤ የተሳተፉ ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች፣ በግጭቱ ዐውድ ውስጥ የታሰሩ ፖለቲከኞች፣ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዜጎች እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡

ተሳታፊዎቹ፣ በሰላም ጉባኤው ማጠቃለያ ላይ ባወጡት ባለዐሥር ነጥብ የአቋም መግለጫ፣ መንግሥት ታሳሪዎቹን በምሕረት እና በይቅርታ መፍታቱ፣ “ለክልሉ ዘላቂ ሰላም የበኩላቸውን እንዲወጡ ያስችላል፤” ብለዋል፡፡

ጉባኤውን በአዘጋጀው በክልሉ መንግሥት እና በተሳታፊዎች መካከል፣ እስረኞቹ እንዲፈቱ መግባባት ላይ ስለመደረሱ ግን የተገለጸ ነገር የለም፡፡

የግጭት ታሳሪዎች እንዲፈቱ፣ በሰላም ጉባኤው የአቋም መግለጫ ላይ የቀረበው ጥያቄ፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በዐማራ ክልል ላይ የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ፣ ባለፈው ግንቦት ወር መጨረሻ ማብቃቱን አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ እንደሚያንጸባርቅ፣ በኮሚሽኑ የሪጅን ዲሬክተር አቶ ዓለሙ ምሕረት አመልክተዋል፡፡

The code has been copied to your clipboard.

width px height px

No media source currently available

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ/አብን/ ፓርቲን በመወከል ከክልሉ ተመርጠው ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የገቡት አቶ አበባው ደሳለው፣ መንግሥት ራሱ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ የግጭት ታሳሪዎች እንዲፈቱ የሚጠይቅ የአቋም መግለጫ ማውጣቱ፣ ታሳሪዎችን ለመፍታት ዕቅድ እንዳለው የሚያሳይ ነው፤ ብለዋል፡፡

People are also reading