Home Back

በመግባቢያ ስምምነቱ ላይ ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ኢትዮጵያ ገለጸች

voanews.com 2024/10/5
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ

ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋራ የተደረገውን የመግባቢያ ስምምት በተመለከተ፣ በማኅበራዊ የመገናኛ አማራጮች የሐሰት መረጃዎች እየተሰራጩ ናቸው፤ ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያ የመግባቢያ ስምምነቱን ለመሰረዝ እንደወሰነች”

“ኢትዮጵያ የመግባቢያ ስምምነቱን ለመሰረዝ እንደወሰነች” የሚገልጽ ይዘት ያለው መረጃ መሰራጨቱን ተከትሎ፣ ትላንት ረቡዕ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መግለጫ ሰጥቷል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ፣ የመግባቢያ ስምምነቱ የሚገኝበትን ደረጃ በተመለከተ “ወቅቱ ሲደርስ ይገለጻል” ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

በተያያዘ ቃል አቀባዩ፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ ግዛት ጥሰው እንደገቡ፣ በሶማሊያ በኩል የቀረበውን ክስም “ሐሰት ነው” ሲሉ አጣጥለዋል፡፡

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

People are also reading