Home Back

በክልሎች ደረጃ የሚደረገው የውይይት ምዕራፍ በአዲስ አበባ ሊጀመር ነው

voanews.com 2024/7/1
በክልሎች ደረጃ የሚደረገው የውይይት ምዕራፍ በአዲስ አበባ ሊጀመር ነው

በኢትዮጵያ በክልሎች ደረጃ የሚከናወነው የሀገራዊ ምክክር ምዕራፍ፣ በመጪው ረቡዕ በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚጀመር ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

ኮሚሽኑ፣ ዛሬ ሰኞ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ፣ ከነገ በስቲያ ግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም. በሚጀምረው የርእሰ መዲናዪቱ የምክክር ምዕራፍ፣ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ከ2ሺሕ5መቶ በላይ ተወካዮች ይሳተፉበታል፤ ብሏል፡፡

ኮሚሽኑ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ፣ በቀረው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማዘጋጀት ማቀዱንም፣ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ኂሩት ገብረ ሥላሴ ተናግረዋል፡፡

People are also reading