Home Back

በዋግኽምራ ዞን 15 ሕፃናት በኩፍኝ ወረርሽኝ ሕይወታቸው ማለፉን ጽሕፈት ቤቱ አስታወቀ

voanews.com 2024/7/7
የኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ

በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን መደበኛ ክትባት በመቋረጡ በተከሠተው የኩፍኝ ወረርሽ፣ ባለፈው ወር ብቻ 15 ሕፃናት መሞታቸውን፣ የዞኑ ጤና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ፣ ዛሬ ማክሰኞ ለአሜሪካ ድምፅ እንደገለጹት፣ በአካባቢው በተደጋጋሚ ባጋጠመው የጸጥታ ችግር የተነሣ ሕፃናት በዕድሜያቸው ማግኘት የነበረባቸውን መደበኛ ክትባት አላገኙም።

ከአምስት ወራት በፊት በሰሀላ ሰየምት ወረዳ ብቻ ተከሥቶ የነበረው የኩፍኝ ወረርሽኝ በኹሉም ወረዳዎች በመስፋፋቱ፣ በአሁኑ ሰዓት ሁለት ሺሕ ሕፃናት በወረርሽኙ መያዛቸውን ገልጸዋል።

The code has been copied to your clipboard.

width px height px

No media source currently available

በቅርቡ፣ ለሕፃናቱ በዘመቻ መልክ የክትባት አገልግሎት እንደሚጀመር የጠቆሙት ኃላፊው፣ በጸጥታው ችግር የተነሣ ለባለሞያዎች ተደራሽነት አዳጋች በኾኑ ወረዳዎች ያሉ ሕፃናትን ለመታደግም ረጂ ድርጅቶች ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

People are also reading