Home Back

የ2024 ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ሪፖርት እና የኢትዮጵያ ድርሻ

voanews.com 2024/7/5
መርካቶ ገበያ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
መርካቶ ገበያ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በ11 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን፣ የተባበሩት መንግሥታት ንግድ እና ልማት ኮንፈረንስ አስታወቀ፡፡

ተቋሙ ይፋ ባደረገው፣ የ2024 ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ በ2023 የሳበችው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት፣ 3ነጥብ26 ቢሊዮን ዶላር እንደኾነ ገልጿል፡፡

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

ይህም፣ ካለፈው ዓመት አንጻር ቅናሽ ቢኖረውም፣ በምሥራቅ አፍሪካ ግን ከፍተኛው እንደኾነ አመልክቷል፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ያናገራቸው የኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት ባለሞያዎች በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ ያገኘችው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት፣ አሁን ካለችበት ኹኔታ አንጻር “ከፍተኛ የሚባል መኾኑን” አስረድተዋል፡፡

ለተሻሻለ ውጤት ምክንያቱም፣ ኢኮኖሚውን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት የሚያደርጉ የመንግሥት የፖሊሲ ማሻሻያዎች ሊኾኑ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡

People are also reading