Home Back

የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች አመላለሳቸው በመጓተቱ ችግራቸው መባባሱን ገለጹ

voanews.com 2024/10/5
የኢትዮጵያ ካርታ
የኢትዮጵያ ካርታ

ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በኋላ የይገባኛል ጥያቄ ከሚነሣባቸው የትግራይ እና የአማራ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ሰዎችን የመመለሱ ሥራ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እየተፈጸመ ባለመኾኑ ችግራቸው መባባሱን ተፈናቃዮቹ ተናግረዋል፡፡

ከፀለምቲ ወረዳ መፈናቀላቸውን ለአሜሪካ ድምፅ የገለጹት አስተያየት ሰጭዎቹ፣ እስከ ግንቦት 30 ቀን እንዲመለሱ ለማድረግ ታቅዶ እንደነበር አውስተው፣ እስከ አሁን ግን አለመመለሳቸውንና ከክረምቱ ወቅት መዳረስ ጋራ ተያይዞ ችግራቸው ሊባባስ እንደሚችል አመልክተዋል፡፡

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

በጉዳዩ ላይ፣ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እና ከፌደራል መንግሥት የኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ጽሕፈት ቤት ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡

ኾኖም፣ የክልሉ የሰሜን ምዕራብ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ከላሊ ሓጋዚ፣ በፀለምቲ ወረዳ ከጦርነቱ በኋላ የተመሠረቱ የአስተዳደር እና የጸጥታ መዋቅሮች በፌደራል የጸጥታ ኀይሎች እስከ አሁን እንዲፈርሱ አለመደረጋቸው፣ ለተፈናቃዮቹ በወቅቱ አለመመለስ ምክንያት እንደኾነ ጠቅሰዋል፡፡

People are also reading