Home Back

በመተማ ወረዳ አንዲት ሱዳናዊትን ጨምሮ ሦስት ሰዎች በታጣቂዎች ተገደሉ

voanews.com 2024/7/7
ፎቶ ፋይል፦ መተማ ከተማ
ፎቶ ፋይል፦ መተማ ከተማ

በምዕራብ ጎንደር ዞን፣ ባለፈው ሳምንት እሑድ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ፣ አንዲት ሱዳናዊት ስደተኛን ጨምሮ ሁለት ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን፣ የመተማ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ሞገስ ግድያው የተፈጸመው፣ ከምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና ከተማ ገንደ ውኃ ወደ ነጋዴ ባሕር ሲጓዝ በነበረ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ላይ በተከፈተ ተኩስ እንደኾነ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

የግድያ ድርጊቱን፣ የኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎትም አረጋግጧል፡፡

People are also reading