Home Back

የዐማራ ክልል ግጭትን ለመፍታት የተቋቋመው የሰላም ምክር ቤት የድርድር ጥረት መጀመሩን አስታወቀ

voanews.com 2024/10/6
ፎቶ ፋይል፦ ባህር ዳር፤ ኢትዮጵያ
ፎቶ ፋይል፦ ባህር ዳር፤ ኢትዮጵያ

የዐማራ ክልል መንግሥት በቅርቡ ባዘጋጀው የሰላም ኮንፍረንስ ተሳታፊዎች የተቋቋመው "የሰላም ምክር ቤት"፣ በመንግሥት እና በፋኖ ታጣቂ ቡድን መካከል የሰላም ድርድር ለማድረግ ጥረት መጀመሩን አስታወቀ።

የምክር ቤቱ አባላት፣ ባለፈው ቅዳሜ በባሕር ዳር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በሁለቱ ወገኖች መካከል ሊኖር የሚችለውን ድርድር የማሳለጥ ኃላፊነት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

የሰላም ምክር ቤቱ፣ በመንግሥት በተዘጋጀ ጉባኤ የተቋቋመ መኾኑን የገለጹ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው አንዳንድ የክልሉ ነዋሪዎች፣ በገለልተኛነቱ ላይ ጥያቄ አንሥተዋል። ሌሎች ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ የተጀመረው ጥረት ሰላም እንዲያመጣ ምኞታቸው ገልገልጸዋል።

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

People are also reading