Home Back

ለሰላም ድርድር አሁንም ዝግጁ መኾኑን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አስታወቀ

voanews.com 2024/7/3
ለሰላም ድርድር አሁንም ዝግጁ መኾኑን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አስታወቀ

በኦሮሚያ ክልል የቀጠለውን የጸጥታ ችግር በውይይት ለመፍታት ክልላዊ መንግሥቱ አሁንም እንደሚሠራ፣ የክልሉ ብልጽግና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈቃዱ ተሰማ ገልጸዋል።

የክልሉ አስተዳደር፣ ትላንት እሑድ፣ በክልሉ ይንቀሳቀሳሉ ከተባሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋራ በአዲስ አበባ ምክክር አድርጓል።በምክክሩ የተሳተፉት፣ የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዚዳንት እና የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሰሎሞን ታፈሰ፣ በውይይቱ ላይ ሰላምንና ጸጥታን እንዲሁም ልማትን የሚመለከቱ ጉዳዮች መነሣታቸውን ገልጸዋል። ይኹንና፣ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ/ኦፌኮ/ እና ኦነግ በውይይቱ አለመሳተፋቸውን አክለው ተናግረዋል፡፡

People are also reading