Home Back

የካሳ ክፍያ የዐዋጅ ማሻሻያው “የመብት ጥሰትን ያስከትላል” ሲል ኢሰመኮ ተቸ

voanews.com 2024/7/8
ፎቶ ፋይል፦ሸማቾች ከአፍሪካ ትልቁ ገበያ በሆነው መርካቶ ውስጥ ይገበያያሉ፤ እአአ ሚያዚያ 25/2024
ፎቶ ፋይል፦ሸማቾች ከአፍሪካ ትልቁ ገበያ በሆነው መርካቶ ውስጥ ይገበያያሉ፤ እአአ ሚያዚያ 25/2024

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ትላንት ማክሰኞ የጸደቀው፣ የመሬት ይዞታ ካሳ ክፍያ የዐዋጅ ማሻሻያ፣ የመብት ጥሰትን ያስከትላል፤ ሲል ተችቷል፡፡

ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትን፣ ካሳ የሚከፈልበትንና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ኹኔታ የሚወስነው የዐዋጁ ማሻሻያ፥ የካሳ ክፍያን፣ ከፌዴራሉ መንግሥት ወደ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ማሸጋገርን ጨምሮ ከዳኝነት ጉዳዮች ጋራ የተገናኙ ለውጦችንም ደንግጓል፡፡

ይህም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄ አሥነስቷል፡፡

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

ማሻሻያው፣ በቀድሞው ዐዋጅ ላይ ያሉ ለባለይዞታዎች ጠቃሚ የኾኑ ድንጋጌዎችን ወደ ኋላ ይመልሳል፤ ሲሉ፣ የኢሰመኮ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ መብቶች ሥራ ክፍል ዲሬክተር ዶር. ብራይትማን ገብረ ሚካኤል ተናግረዋል፡፡

People are also reading