Home Back

በኢትዮጵያ አራት ክልሎች ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ተካሔደ

voanews.com 2024/7/3
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኀይሉ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኀይሉ

በኢትዮጵያ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልን ጨምሮ በአራት ክልሎች፣ ትላንት እሑድ፣ የስድስተኛው ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ መካሔዱን፣ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኀይሉ፣ የምርጫውን መጠናቀቅ አስመልክተው፣ ትላንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ምርጫው፥ በቤንሻንጉል ጉምዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች መከናወኑን ተናግረዋል።

The code has been copied to your clipboard.

No media source currently available

በጸጥታ ችግር ምክንያት ምርጫ ያልተካሔደባቸው 40 የምርጫ ጣቢያዎችም እንዳሉ ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።

ምርጫው በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ሲካሔድ፣ ከ10 ዓመታት በኋላ እንደኾነ ያመለከተው የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ ሕዝቡ የሚፈልገውን መሪ ለመምረጥ ዕድል መስጠቱን ጠቅሶ፣ ሒደቱም በሰላም መጠናቀቁን ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቋል፡፡

People are also reading