Home Back

ፓርቲዎች ዳግም ሕጋዊ እውቅና እንዲያገኙ የሚያስችል የዐዋጅ ማሻሻያ ጸደቀ

voanews.com 2024/7/8
ፓርቲዎች ዳግም ሕጋዊ እውቅና እንዲያገኙ የሚያስችል የዐዋጅ ማሻሻያ ጸደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ በዐመፅ ተግባር ላይ ተሳትፈዋል የተባሉ ፓርቲዎች ዳግም ሕጋዊ እውቅና እንዲያገኙ የሚያስችል የዐዋጅ ማሻሻያ ዛሬ አፀደቀ።

የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶር. ጌዲዮን ጢሞቴዎስ፣ ዐዋጁ አገራዊ ምክክሩን ታሳቢ በማድረግ መሻሻሉን ገልጸዋል፡፡ በዚኽም፣ ህወሓት እና በዐመፅ ተግባር ሲሳተፉ ነበሩ የተባሉ ፓርቲዎችን፣ እንዲሁም በትጥቅ ግጭት ውስጥ ያሉ ቡድኖችን ወደ ምክክር ሒደቱ ለማምጣት መታለሙን ተናግረዋል፡፡ በዐዋጁ ማሻሻያ ላይ፣ ከምክር ቤት አባላት የድጋፍ እና የተቃውሞ አስተያየቶች ተሰንዝረዋል፡፡

People are also reading